loader image

በሰብአዊ መብት ጉዳዮች ላይ በባለድርሻ አካላት ዘንድ የጋራ ግንዛቤ መፍጠሪያ ዐውደጥናት

በሰብአዊ መብት ጉዳዮች ላይ በባለድርሻ አካላት ዘንድ የጋራ ግንዛቤ መፍጠሪያ ዐውደጥናት

ድርጅታችን ሴንተር ፎርዴቬሎፕሜንት ኤንድ ካፓሲቲ ቢልዲንግ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ቅድሚያ ከሰጣቸው ጉዳዮች መካከል የሰብአዊ መብት ጉዳዮች ይገኙበታል፡፡ በዚሁ መሰረት ሲዲሲቢ በሰብአዊ መብት ጉዳዮች, በሰላም መስፈንና በመልካም አሰተዳደር ረገድ በማህበራዊ ሚዲያ በሚገባ ለመገልገል እንዲያስችለው በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ‘የመስመር ላይ ወጣት ማህበረሰብን’ አቋቋሟል፡፡ በዚህ ረገድ የሰብአዊ መብት አያያዝን ለማጠናከርና ብዙ ተከታይ ወጣቶችን አፍርቶ የበለጠ ተዕእኖ ለመፍጠር እንዲቻል ሚያዝያ 2015 ዓ.ም. የማህበራዊ ሚዲያ (ፌስቡክ) ወር ብለን ሰይመናል፡፡ እንቅስቃሴው ወድድርን/ፈተናን (challeges) , ወቅታዊ የመረጃ ልውውጥንና የምክክር ዐውደጥናቶች ያካትታል፡፡ ይህ ዐውደጥናት የሰብአዊ መብት ጉዳዮችን አያያዝን በማሳደግና በመከላከል ረገድ በባለድርሻ አካላት አመራር እና በወጣቱ ዘንድ የብዙሃን የሰብአዊ መብት ጉዳዮች ተገቢውን ግንዛቤ እንዲያገኝ የማህበረሰቡን የተባበረ ጥረት የመሳብ አካል ነው፡፡  

ማዕከሉ ለሰብአዊ መብት ጉዳዳች ቅድሚያ የሰጠው ለሰላም ግንባታና በአገርአቀፍ ደረጃ በተለያዩ ማህበረሰቦች ዘንድ መተማመንን ለመፍጠር በማሰብ ነው፡፡ የሰብአዊ መብት ጥሰት ያለ ጥርጥር ወደ አለመግባባትና ሽብር የሚያመራ በመሆኑ የሰብአዊ መብት ጉዳዮች የሲዲሲቢ ብቻ ሳይሆን በይበልጥም በመንግስትና በሌሎች ባለድርሻ አካላትም ቅድሚያ የሚሰጠው ነው፡፡ ሽብር በሰዎች ሞትና በንብረት ውድመት የሚከሰት ጥፋትን ያስከትላል፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ጥፋት ደግሞ በተደጋጋሚ ሽብርን በሽብር የመመለስ መበቃቀልና የማህበረሶችን መበታተን ሊያስከትል ይችላል፡፡   

በመሆኑም ሲዲሲቢ ከለጋሽ ድርጅቶች በተለይ ከናሽናል ኢንዶውሜንት ፎር ዲሞክራሲ (ኔድ) እና ከሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት ጋር በመተባበር በዲጅታል መድረክ አማካይነት የሕዝቡን የንቃት ደረጃ ለማሳደግ በሰፊው ሲሰራ ቆይቷል፡፡ የዚህ ዐውደጥናት ውጤትም የሰብአዊ መብትን አያያዝ በማጠናከር ዘላቂ የሆነ በጎ ተዕእኖ ለመፍጠር በሁሉም የሚዲያ አውታሮች በተደጋጋሚ እንደሚሰራጭ ተስፋ እናደርጋለን፡፡

Previous Youth Leaders experience sharing under way in Adama

Connect With Us

Meskel Square Science and Technology Building 5th Floor

Mon – Fri: 8:00 am – 5:00 pm

P.O. Box: 25024 Code 1000

Join the Community

Get latest CDG news, articles, and resources, sent straight to your inbox every month.

Copyright © 2022 CDCB | Powered by CDCB