loader image

የወጣት መሪዎች ምክክር በአገር ጉዳይ ላይ

img_home3_1

የወጣት መሪዎች ምክክር በአገር ጉዳይ ላይ

ወጣት መሪዎች በመልካም አስተዳደር እና በሰላም ላይ ያላቸውን ሚና ለማጉላት የሚያስችል የ4 ቀናት ምክክር መድረክ ከትናት ጀምሮ በቢሾፍቱ/ደብረዘይት ድሪምላንድ ሪዞርት ሆቴል በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ ይህ ለሁለተኛ ዙር በመካሄድ ላይ የሚገኘው የምክክር መድረክ የሚወያይባቸው ጉዳዮች የፌደራል አስተዳደርን ዲሞክራሲን ሰብአዊ መብቶችን እና ሰላምን የሚያካትት ነው፡፡ የምክክር መድረኩ የተዘጋጀው ዋና ጽ/ቤቱ ካናዳ በሚገኘው የፌዴሬሽች ፎረም እና በሴንተር ፎር ዲቨሎፕሜንት ኤንድ ካፓሲቲ ቢልዲንግ አገር በቀል መያድ የጋራ ቀንጅት ነው፡፡

 

img_home3_2

በመድረኩ መክፈቻ ላይ የተከበሩ አቶ ታየ ደንዳአ የሰላም ሚኒሰቴር ሚኒስትር ዴታ ነበሩ፡፡ ሚኒስትር ዴታው የመድረኩ ተሳታፊ ወጣቶች በአራት ቀናቱ ውይይታቸው ወቅት የውይይቱ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑና አገሪቱን በአሁኑ ወቅት የገጠሟትን ፈታኝ ሁኔታዎች በጋ ለመፍታት በሚያስችሉ እሴቶች ታጥቀው ወደየመስካቸው እንዲመለሱ አበረታተዋል፡፡

አቶ ደሳ ቡልቻ የፌዴሬሽኖቹ ከፍተኛ ዳይሬክተር በፌዴሬሽኖቹ ላይ እና ሲዲሲቢ ሥራውን ለማከናወን ፍላጎት እና ዝግጁነቱን በማሳየቱ ከነሱ ጋር ይህ  ሥልጠና መዘጋጀቱን አስመልክተው አንዳንድ የዳራ ነጥቦችን አመልክተዋል፡፡

አቶ አማኑኤል አድነው የሲዲሲቢ ዋና ዳይሬክተር በበኩላቸው ተሳታዎችን እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት ተቀብለው ስለሲዲሲቢ እና ስለሥልጠናው አንዳንድ አጠቃላይ ጉዳዮችን አንስተዋል፡፡ በዚሁ ንግግራቸው ሴንተሩ የሀገሪቱን ችግሮች ለመፍታት የሚያስችሉ አግባብነት ያላቸው ጥናቶች እንዲካሄዱ የቡሉን ጥረት ሲያደርግ እንደነበር ተናግረዋል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ ሲዲሲቢ ወቅታዊ ጉዳዮችን በሚመለከት ምሁራንን እና ታዋቂ ሰዎችን ያሳተፉ ልዩ ልዩ መድረኮችን ሲያዘጋጅ መቆቱን አብራርተዋል፡፡ አሁን እየተካሄደ ያለውን ሥልጠና አስመልክተውም ጥናቱ የተዘጋጀው ለዚሁ ሲባል የተናቀረውን የጥናት ማኑዋል መሰረት አድርጎ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ሥልጠናው በቀጣይ 3 ሳምንታትም በተከታታይ ከማክሰኞ እስከ አርብ በሚኖሩት ቀናት በሌሎች 3 የሠልጣኞች ቡድን እንደሚቀጥል ለማወቅ ተችሏል፡፡

Previous The Second Day youth leadership Dialogue skill training.

Connect With Us

Meskel Square Science and Technology Building 5th Floor

Mon – Fri: 8:00 am – 5:00 pm

P.O. Box: 25024 Code 1000

Join the Community

Get latest CDG news, articles, and resources, sent straight to your inbox every month.

Copyright © 2022 CDCB | Powered by CDCB